Category Archives: News

ነሐሴንና ጳጉሜን የአዲስ የቤተክርስቲያን አባላት የትውውቅ ጊዜ እና የነባር የደብራችን አባላት የእንቅስቃሴ ወሮች እንዲሆኑ ስለማቀድ

በኢትዮጵያ አቆጣጠር የ2015 ዓ.ም.ን መገባደጃ በመንተራስ በቀሪዎቹ የነሐሴና ጳጉሜ ወሮች የአዲስ የቤተክርስቲያን አባላት የትውውቅ ጊዜ እና የነባር የቤተክርስቲያን አባላት እንቅስቃሴ መርኅግብሮች እንዲታቀዱ የአስተዳደር ቦርዱ ወስኖ የሚከተሉት መርኅግብሮች እንዲከናወኑ ይሆናል:: አዲስ የቤተክርስቲያን አባል ማለት በኢትዮጵያ አቆጣጠር የ2015 ዓ.ም የደብራችን አባል የሆኑ ማለት ነው::

የአዲስ አባላት የትውውቅ መርኅግብር:-

  1. እሁድ እሁድ ከቅዳሴ አገልሎት ፍፃሜ በሗላ እታች አዳራሽ ውስጥ አዲስ የቤተክርስቲያን አባሎቻችንን የእንኳን የደብራችን አባል ሆናችሁ በማለት የካህናት የአስተዳደር ቦርድ እና የአባላት ማኅበራት ተወካዮች ጋር ትዉዉቅ ይደረጋል::
  2. የእዲስ አባላት ስም ዝርርዝም እታች አዳራሽ ውስጥ በሚገኘው ቴሌቪዥን ስኪሪን ላይ ይተላለፋል::
  3. የቤተክርስቲያን አባልነት መታወቂያ ካርድ ላልወስዱ በእለቱ የቤተክርስቲያን አባልነት መታወቂያ ካርድ እንዲያወጡ ይደረጋል::
  4. በእለቱም ለ ዲስ አባላት ቡና ሻይና ዳቦ ካለ ይቀርባል::

የነባር የደብራችን አባላት እንቅስቃሴ መርኅግብር:-

  1. ነባር የቤተክርስቲያን አባሎች እሁድ እሁድ አታች አዳራሽ ውስጥ በሚገኘው የቦርድ አባላት የጠረጴዛ ቢሮ ድረስ በመሄድ የአባላት መዝገብ ላይ ያለው አድራሻችሁ ስልክ ቁጥራችሁና ኢሜል ትክክል እንደሆነ እንድታረጋግጡልን በአክብሮት እንጠይቃለን::
  2. የደብራችን አባልነት አዲስ መታወቂያ ካርድ ያላወጡ በእለቱ የቤተክርስቲያን አባልነት መታወቂያ ካርድ እንዲያወጡ ይደረጋል::
  3. የየደብራችን አባልነት የወርሀዊ መዋጮአችሁ መጠናቀቁን የቦርድ አባላትን መጠየቅና ውዝፍ ካለ በወቅቱ እንዲጠናቀቅ መሞከር
  4. የደብራችን አባል ያልህኑ ዘመዶች ጏደኞች እና ወዳጆችን የቤተክርስቲያኗ አባል እንዲሆኑ ማነቃቃትና ማበረታታት
  5. የቤተክርስቲያናችን የመረዳጃ ማህበር አባል ለመሆን መሞከር
  6. ገቢው ለአዲስ ቤ.ክ. ማስሪያ የሚውል የበጎፍቃድ ስራ አገልግሎት ላይ ለመሳተፍ ከፕሮግራሙ እስተባባሪ ከዶ/ር አሻግሬ መረጃ መጠየቅ

መርኅግብሮቹ ከመጪው እሁድ የቅዳሴ አገልሎት ፍፃሜ በሗላ ለአምስት ተከታታይ እሁዶች የምንከታተላቸው ይሆናል:: ቀኖቹም ነሐሴ7(Sug 13), ነሐሴ14(Aug 20), ነሐሴ21(Aug 27), ነሐሴ28(Sep 3), ጳጉሜ5(Sep 10) ናቸው::

ያቀድናቸውና ያሰብናቸው እንዲሳኩ ውድ የደብራችን ነባርና አዲስ የቤተክርስቲያን አባላት ከምንጊዜውም በበለጠ ሁኔታ የሰበካ ጉባዔውን እንድትተባበሩት በትህትና እንጠይቃለን:: በፅሁፍም ሆነ የመረጡትን የሰበካ ጉባዔ አባል በግል በመቅረብ አዳዲስ የአሰራር ሃሳቦችን እንድታካፍሉን ይሁን::

የደብራችን 2023 ተመራቂ ተማሪዎች እና ቤተሰቦች እንኳን ደስ ያላችሁ ! / Congratulations to 2023 Grads & Families!

“ከእግዚአብሔር ቤት መረቅናችሁ” መዝ.118:26

በዘንድሮው የ2023 ዓ.ም. የ12ኛ ክፍልን እና የከፍተኛ ትምህርትን ላጠናቀቁ የቤተክርስቲያናችን ወጣቶች የእንኳን ደስ ያላችሁ የምስክር ወረቀት ቤተክርስቲያናችን ባለፈው እሁድ ሐምሌ 30 (Aug 6, 2023) አበርክታለች:: የሚቀጥለው የትምህርትና የመደበኛ ስራ ዘመናቸውም የተቃና እንዲሆንላቸውም ከእግዚያብሔር ቤት ተመርቀዋል::

Congratulations to 2023 grads and families. Graduates were handed out congratulating certificates by our church during the Sunday church services on Aug 6, 2023.

የደብራችን 2023 ተመራቂ ተማሪዎች እና ቤተሰቦች በድጋሚ እንኳን ደስ ያላችሁ !

ጾመ ፍልሰታ / የነሐሴ ቅዳሴ አገልግሎት ቀኖች እና የበጎፈቃደኝነት አገልግሎት ቀኖች / DSMA Calendar of Activities in August 2023

ከነሐሴ 1 እስከ ነሐሴ 16 (Aug 7 – Aug 22) ጾመ ፍልሰታ ሙሉ ቅዳሴ አለ

የንግሥ በአላት ፀሎት እና ቅዳሴ አገልግሎቶች / Annual Holidays and Celebrations with Liturgical services ነሐሴ 13 (Aug 19) – ደብረ ታቦር (Transfiguration- Debre Tabor)
ነሐሴ 16 (Aug 22) የነሐሴ ኪዳነምህረት ንግስ (The assumption of Virgin Mary)


የአዘቦት ቅዳሴ አገልግሎት ቀኖች ( Covenant prayer services)
ነሐሴ 12, ነሐሴ 19, ነሐሴ 21, ነሐሴ 27 (Aug 18, Aug 25, Aug 27, Sep 2)

የበጎፈቃደኝነት አገልግሎት ቀኖች / Volunteer Services dates for fundraising
. At the US Bank Stadium : Aug, 12, Aug 19 & Aug 26
. At the State Fair Parking : Aug 26 & Aug 27, Sep 2 to Sep 4

July 29, 2023 ልናደርገው የነበረው የገንዘብ ማሰባስብ እቅዳችንን ለመሰረዝ ተገደናል / BCC FUNDRAISER AT THE ETHIOPIA DAY IN MINNESOTA IS CANCELLED

የቤተክርስትያናችን የህንጻ ግንባታ ኮሚቴ አባላት July 29, 2023 በሚኒሶታ የኢትዮጵያ ቀን አከባበር ሜዳ ላይ ተገኝተዉ ምግብ መጠጥ እና ሌሎች ቁሳቁሶችን በመቨጥ ለአዲስ ቤተክርስቲያን ሕንፃ ግንባታ የሚዉል ገንዘብ እንደሚያሰባስቡና እናንተም እንድትጐቦኟቸው የሚል ማስተወቂያ በዚህ ገጽ ላይ መለጠፋችን ይታወሳል::

ነገር ግን ከዚህ በፊት ባልታዩ ምክኒያቶች ብቻ በሚኒሶታ የኢትዮጵያ ቀን አከባበር ሜዳ ላይ ተገኝተን ልናደርገው የነበረው የገንዘብ ማሰባስብ እቅዳችንን ለመሰረዝ ተገደናል:: ከይቅርታ ጋር!

Due to unforeseen circumstances, the upcoming BCC grill fundraiser event at the Minnesota Ethiopia Day celebration on July 29, 2023 is cancelled. Please accept our apology.

የዘንድሮዉ ዓመት የቅዱስ ገብርኤል በዓለ ንግስ እና የዋዜማ አገልግሎት፣ ሐምሌ 15 እና ሐምሌ 16, 2015 በሚኒሶታ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ይከበራል:: The annual Hamle Gebriel celebration will be on July 22 & July 23, 2023.

የዋዜማዉ አገልግሎት በመጪዉ ቅዳሜ ሐምሌ 15, 2015 (Saturday July 22, 2023) ከ 4pm ጀምሮ ይከበራል::

የማኅሌት አገልግሎት በመጪዉ እሁድ ሐምሌ 16, 2015 (Sunday July 23, 2023) ከንጋቱ 2 am ጀምሮ ይሰጣል::

ከቤተሰብ፣ ከዘመድ እና ከወዳጅ ጋር በመምጣት የቅዱስ ገብርኤልን በረከት ይካፈሉ ዘንድ ቤተክርስቲያናችን ጥሪዋን ታስተላልፋለች።

አድራሻችን: 4401 Minnehaha Avenue S., Minneapolis, MN
55406

የዘንድሮዉ ዓመት የ5,000 ሜትር ርቀት ሩጫና እርምጃ መርኃ ግብር በደመቀ መልኩ በሰላም ተጠናቀቀ / This year’s 5K run and walk was a successful event

የሚኒሶታ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን አባላት እና ቤተሰቦቻቸው ቅዳሜ ሰኔ 24 2015 (July 1st, 2023) በፌለን መናፈሻ ውስጥ ለዘጠነኛ ጊዜ የተዘጋጀውን የ5,000 ሜትር ሩጫና እርምጃ መርኃ ግብር በደመቀ መልኩ ተሳትፈው መርኃ ግብሩ በሰላም ተጠናቋል::

Members, families and friends of Debre Selam Medhanealem Ethiopian Orthodox Tewahedo Church in Minnesota came out in large numbers at the 9th annual 5K run and walk on July 1st, 2023 at Phalen Park, St Paul, Minnesota.

በእለቱም አሸናፊዎች የተዘጋጀላቸውን ሜዳልያና ምስክር ወረቀት ከደብራችን አስተዳዳሪ ከመልአከ ጽዮን ቀሲስ አዲስ ሞላው እና ከመርኃ ግብሩ አዘጋጆች ተቀብለዋል::
5K run and walk winners were recognized with medals and certificates from the head priest, Meleake Tsion Kesis Addis Molaw and event organizers.

Class of 2023 5K Run/Walk Winners

Females: 15 – 30 years old Group
1st. Yeabsra Berhanu / የብስራ ብርሃኑ
2nd. Mena Feleke / መና ፈለቀ
3rd. Lia Lantyderu / ሊያ ላንተይደሩ

Males: 15 – 30 years old Group
1st. Bisrat Gebre / ብሰራት ገብሬ
2nd. Kaleab Assefa / ካሌብ አሰፋ
3rd. Nathan Yohannes / ኔተን ዮሐንስ
4th. Naom Ewinetu / ናኦም እውነቱ

Females: 30+ years old Group
1st. Yeshi Getahun / የሺ ጌታሁን
2nd. Yeshiwork Zenebe / የሺወርቅ ዘነበ
3rd. Tigist Mengistu / ትእግስት መንግስቱ
4th. Genet Gebremichael / ገነት ገብረሚካኤል

Males: 30+ years old Group
1st. Kinfe Ashu / ክንፈ ኣሹ
2nd. Mitiku Desalegn / ምትኩ ደሳለኝ
3rd. Ephrem Ghida / ኤፍሬም ጊዳ
4th. Tewodros Desta / ቴዎድሮስ ደስታ
5th. Estefanos / እስጢፋኖስ
6th. Dawit Worku / ዳዊት ወርቁ
7th. Ashebir / አሸብር

ከቤተሰብ፣ ከዘመድ እና ከወዳጅ ጋር በመምጣት በመርኃ ግብሩ ተካፊይ ለሆኑ እና ለመርኃ ግብሩ አዘጋጆች በሙሉ ቤተ ክርስቲያን ምሰጋናዋን ታቀርባለች::

Thank you to the church members, families and event organizers who made the 9th 5K run and walk a success!.

በሰሞነ ህማማት የተላለፈው ውግዘት ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን የጣሰ ነው ተባለ

የደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በትላንትናው ዕለት የቅዱስ ሚካኤልን በዓለ ንግስ ተጋባዥ እንግዳ መልአከ ምህረት ቆሞስ አባ ምህረት ዘውዴ በተገኙበት በደመቀና ባማረ መልኩ ያከበረ ሲሆን፤ በዕለቱም በደብረ ሰላም ካህናት ላይ ለምን በዕለተ ሆሳዕና ቀደሳችሁ ፣ ለምን ህዝበ ክርስቲያኑን አሳልፋችሁ ለተኩላ አልሰጣችሁም በማለት በአባ ዘካርያስ የተላለፈው የሰሞነ ህማማት ውግዘት  ኢቀኖናዊ መሆኑን አስተምረዋል።

መልአከ ምህረት ቆሞስ አባ ምህረት ዘውዴ በመቀጠልም በሰሞነ ህማማት እንኳን ውግዘት ማውገዝ ይቅርና ይፍቱህ መባል እንኳን በተከለከለበት ጊዜ ያውም በፀሎተ ሀሙስ ለካህናቱ የውግዘት ደብዳቤ መስጠት የቤክርስቲያንን ህግ የጣሰ መሆኑን ለተሰበሰበው ምዕመናን አስረድተዋል። የምስልና የድምጽ እንዲሁም ዝርዝር ዘገባውን ይዘን እንመለሳለን።

cdlabelየቤተ ክርስቲያኗ ምዕመናን የመልአከ ምህረት ቆሞስ አባ ምህረት ዘውዴ ስብከት በዲቪዲ ተባዝቶ አንዲቀርብላቸው በጠየቁት መሰረት በትላንትናው ዕለት ማለትም እሁድ ነሐሴ 28 2007 ወይንም July 5, 2015 የመጀመሪያውን ዙር ያከፋፈልን ሲሆን በተከታታይ ሳምንታትም ሁሉም ምዕመን እስኪዳረስ ድረስ አቅርቦቱ የሚቀጥል መሆኑን በታላቅ አክብሮት እንገልፃለን።

                            የደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን 

Candlelight Vigil and Prayer Services in State Capitol and DSMA

LibyaMartyersPrayer2
Click on the image for more pictures

ባለፈው ኃሙስ በእስቴት ካፒቶል በሊቢያ በሰማዕትነት ላለፉት፣ በደቡብ አፍሪካና በየመን በግፍ ለተገደሉት ወገኖቻችን አስር የእምነት ተቋማት መሪዎች በተገኙበት በሚኒሶታ ውስጥ ለመጀመሪያ ግዜ በሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያኖች ተገኝተው የጸሎትና የሻማ ማብራት መርኃ ግብር የከወኑ ሲሆኑ ሁሉም የእምነት አባቶች ለህዝባችን አንድነት ለሀገራች ሰላምን ተመኝተዋል። እንዲሁም እሁድ በደብረሰላም መድኃኔዓለም የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ ክርስቲያን በመቶዎች የሚቆጠሩ የቤ/ ክርስቲያኗ ምዕመናን በተገኙበት ከቅዳሴ በኃላ ፀሎተ ፍትኃት እና የጧፍ ማብራት መርኃ ግብር ተካሒዷል። ፀሎተ ፍትኃቱም እንደተጠናቀቀ በተደረገው የገንዘብ ማሰባሰብ ከ$20,000.00 በላይ ሊሰበሰብ ችሏል። ገንዘቡም በዓለም ዙሪያ በስቃይ ላይ ላሉ ኢትዮጵያዊያኖች መርጃ ይውላል።

የጥምቀት በዓል በደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በደመቀ መልኩ ተከበረ

Video 1 

Video 2

ጥር 11 ቀን 2007 ዓ.ም

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን።

Timket5የ2007 ዓ.ም የጥምቀት በአል በሚኒሶታ ደብረሰላም መድኃኔዓለም የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ቁጥሩ በመቶዎች የሚገመት ምእመን በተገኘበት እጅግ ደማቅ በሆነ ኃይማኖታዊ ሥነ ሥርአት ተከበሮ ዋለ። Continue reading የጥምቀት በዓል በደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በደመቀ መልኩ ተከበረ